የሀገር ውስጥ ዜና

ወ/ሮ አዳነች የአረጋዊያን መርጃ ማእከል በመገኘት የበዓል ስጦታ አበረከቱ

By Tibebu Kebede

September 06, 2020

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ አቃቂ ቃሊቲ በሚገኘው የአረጋዊያን መርጃ ማእከል በመገኘት የበዓል ስጦታ አበርክተዋል።

በጉብኝቱ ላይ ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤና በምክትል ከንቲባ ማእረግ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት አስተባባሪ አቶ ጃንጥራር አባይን ጨምሮ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።