የሀገር ውስጥ ዜና

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፈቂ ጋር ተወያዩ

By Tibebu Kebede

December 20, 2019

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 10፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፈቂ ማህማት ጋር ተወያዩ።

በውይይታቸው በአፍሪካ ህብረት 33ኛው የመሪዎች ጉባኤ ቅድመ ዝግጅት፣ በአካባቢያዊ የፖለቲካና የጸጥታ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል።