የሀገር ውስጥ ዜና

የሀረማያ ዩኒቨርሲቲ ለ700 ሺህ አርሶ አደሮች የተሻሻሉ የስኳር ድንች ዝርያዎችን እያሰራጨ መሆኑ ተገለጸ

By Meseret Demissu

September 07, 2020

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 2፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሀረማያ ዩኒቨርሲቲ በምስራቅና ምዕራብ ሀረርጌ ለ700 ሺህ አርሶ አደሮች የተሻሻሉ የስኳር ድንች ዝርያዎችን እያሰራጨ መሆኑን አስታወቀ።

የዩኒቨርሲቲው የተመራማሪዎችና የአርሶ አደሮች የምርምር ቡድን አባላት በባቢሌ ወረዳ እየተካሄደ ያለውን የስኳር ድንች ልማት ትላንት በመስክ ጎብኝተዋል ።