የሀገር ውስጥ ዜና

በአዲሱ ዓመት የህግ የበላይነት በማስከበር የዜጎችን ደንህነት ለማረጋገጥ አጥብቆ እንደሚሰራ የብልፅግና ፓርቲ ገለፀ

By Tibebu Kebede

September 08, 2020

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 3፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) 2013 ዓ.ም ዜጎች በሰላም ወጥተው የሚገቡበት እና ኢትዮጵያውያን በየትኛውም የሀገሪቱ አቅጣጫ ሄደው ሃብት የሚያፈሩበት ለማድረግ እንደሚሰራ የብልጽግና ፓርቲ ገለጸ።

የፓርቲው የውጭ እና አለም አቀፍ ግንኙነት ሃላፊ ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ባደረጉት ቆይታ፥ በተጠናቀቀው ዓመት የብልጽግና ፓርቲ አለም አቀፍና ሃገራዊ ፈተናዎቹን አልፎ ድንቅ ውጤት አስመዝግቧል ብለዋል።