የሀገር ውስጥ ዜና

በመንግስት ሆስፒታሎች የኩላሊት እጥበት ህክምና ለሚከታታሉ ዜጎች ወጪያቸው በመንግስት ይሸፈናል-ወ/ሮ አዳነች አቤቤ

By Meseret Demissu

September 09, 2020

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በ2013 ዓ.ም መንግስት ሆስፒታሎች የኩላሊት እጥበት ህክምና ለሚከታታሉ ዜጎች አመቱን ሙሉ የህክምና ወጪያቸው በመንግስት የሚሸፈን መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

ምክትል ከንቲባዋ የምስጋና ቀንን ምክንያት በማድረግ የዘውድቱ ሆስፒታል ለይቶ ማቆያን ጎብኝተዋል።