የሀገር ውስጥ ዜና

በአማራ ክልል ለ14 ሆስፒታሎች የደረጃ እድገት ተሰጠ

By Meseret Demissu

September 09, 2020

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአማራ ክልል ጤና ቢሮ የ14 ሆስፒታሎችን ደረጃ ማሳደጉን አስታውቋል።

በዚህም በክልሉ 12 ሆስፒታሎችን ከመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ወደ ጠቅላላ ሆስፒታል፣ ሁለት ጠቅላላ ሆስፒታሎችን ደግሞ ወደ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ማሳደጉን ገልጿል።