ቢዝነስ

ንግድ ባንኮች ከሚያቀርቡት ብድር 5 በመቶውን በተንቀሳቃሽ ንብረት ለሚሰጥ የብድር አይነት እንዲያውሉት የሚያዝ መመሪያ ወጣ

By Tibebu Kebede

September 09, 2020

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ የሚገኙ ንግድ ባንኮች ከሚያቀርቡት ብድር 5 በመቶውን በተንቀሳቃሽ ንብረት ለሚሰጥ የብድር አይነት እንዲያውሉት የሚያዝ መመሪያ ማውጣቱን ብሄራዊ ባንክ አስታወቀ።

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ተንቀሳቃሽ ንብቶሮችን በዋስትና አስይዞ መበደር የሚያስችለው መመሪያ ላይ ከፋይናንስ ተቋማት ተወካዮች ጋር ውይይት አካሂዷል።