አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ አደም ፋራህ አዲሱን አመት በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ሊጠናቀቅ አንድ ቀን በቀረው ዓመት ዓለም አቀፋዊ ከሆነው ኮቪድ-19 ወረርሽኝ ላይ ሌሎች ውስጣዊና ውጫዊ ተግዳሮቶች ተጨምረውበት እቅድ አፈጻጸሞቻችንን ከባድ ቢያደርጉም ያጋጠሙ ፈተናዎችን በመቋቋም የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ፍትሓዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ስኬቶችን የተመዘገቡበት አመት ነበር ብለዋል፡፡