አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በ2013 ዓ.ም በኢትዮጵያ የብልጽግና መሰረትን የመጣል ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የብልጽግና ፓርቲ አስታወቀ፡፡
የፓርቲው የጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ብናልፍ አንዱአለም ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንዳሉት፥ 1 ቀን ብቻ በቀረው 2012 ዓ.ም የሀገሪቱን ህልውና የተፈታተኑ ችግሮችን መሻገር ተችሏል። ለውጡን ለማደናቀፍ እና በሀገር ህልውና ጭምር የመጣ የጥፋት እንቅስቃሴ ሀገሪቱን ዋጋ አስከፍሎ አልፏል።