የሀገር ውስጥ ዜና

ከዘመን ወደ ዘመን የምናደርገው ሽግግር ትርጉም እንዲኖረው አዲስና ተራማጅ አስተሳሰብን ልንላበስ ይግባል – ጠ/ሚ ዐቢይ

By Tibebu Kebede

September 10, 2020

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ ዓመት ዋዜማ በዓል ዛሬ በተመረቀው ሸገር ፓርክ የወዳኝነት አደባባይ በድምቀት ሲከበር የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የአዲስ ዓመት የመልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።

በመልዕክታቸው አዲስ ዓመት አዲስ ተስፋን ለመቀበል የዋዜማ ምሽት ላይ እንገኛለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ከፊታችን ምንም ያልተፃፈበት የዘመን መፅሃፍ ተዘርግቷልና እንኳን አደረሰን እንኳን አደረሳችሁ ብለዋል።