የሀገር ውስጥ ዜና

ወይዘሮ አዳነች አቤቤ 300 ዊልቸሮችን ለአካል ጉዳተኞች አበረከቱ

By Feven Bishaw

September 11, 2020

አዲስ አበባ፣ መስከረም 1፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ አዲስ አመትን በማስመልከት 300 ዊልቸሮችን ለአካል ጉዳተኞች አበረከቱ።

የአካል ጉዳተኛ ተሽከርካሪዎቹ ኢንተርናሽናል ፈንድ ፎር አፍሪካ ከተባለ ግብረሰናይ ድርጅት የተገኙ መሆናቸው ታውቋል፡፡