አዲስ አበባ ፣ መስከረም 2 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ከባለቤቱ ጋር በተፈጠረ ጊዜአዊ አለመግባባት የ4 ግለሰቦችን ህይወት መሳሪያ ተኩሶ ያጠፋው የፖሊስ አባል ወዲያውኑ በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
ተጠርጣሪው የግድያ ወንጀሉን የፈፀመው መስከረም 1 ቀን 2013 ዓ.ም ከምሽቱ 2፡30 በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ልዩ ቦታው ጨርጨር ጊርጊሮስ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ መሆኑ ተነግሯል፡፡