የሀገር ውስጥ ዜና

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ከፖርቹጋል አቻቸው ቴሬዛ ሪቤይሮ ጋር ተወያዩ

By Abrham Fekede

September 14, 2020

አዲስ አበባ፣ መስከረም 4፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ከፖርቹጋል አቻቸው ቴሬዛ ሪቤይሮ ጋር በዙም የሁለቱን አገራት ግንኙነት ማጠናከር በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ተወያዩ።

አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን የሁለቱ አገራት ግንኙነት ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ መሆኑን በማስታውስ፤ ፖርቹጋል የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሆና በመመረጧ የተሰማውን ደስታ ገልጸዋል።