የሀገር ውስጥ ዜና

ኤጀንሲዉ በሳይበር ደህንነት ኦዲት 31 የሚሆኑ ተቋማት ላይ የተለያዩ የሳይበር ደህንነት ክፍተቶች መለየቱን ገለጸ

By Meseret Demissu

September 15, 2020

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 5 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ በ2012 የበጀት አመት ባደረገዉ የሳይበር ደህንነት ኦዲት 31 የሚሆኑ ተቋማት ላይ የሳይበር ጥቃት ተጋላጭነት መለየቱን እና እንዲታረሙ ማድረጉን ገለጸ።

በኤጀንሲዉ የሳይበር ደህንነት ኦዲት እና ኢቫልዌሽን ዲቪዥን ሀላፊ የሆኑት አቶ ደሳለኝ ወ/ጊዮርጊስ÷ በተጠናቀቀዉ የ2012 በጀት አመት ኤጀንሲው በ31 የመንግስት እና የግል ተቋማት ላይ ጥልቅ የደህንነት ፍተሻዎችን ማድረጉን ገልጸዋል።