የሀገር ውስጥ ዜና

የአዋሽ ወንዝ ሞልቶ ያስከተለው የጎርፍ አደጋ በርካታ ጉዳቶችን እያደረሰ ነው

By Meseret Demissu

September 15, 2020

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 5 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ ) ዘንድሮ ለየት ባለ ሁኔታ የአዋሽ ወንዝ ሞልቶ ያስከተለው የጎርፍ አደጋ በርካታ ጉዳቶችን እያደረሰ ነው።

ወንዙ አቅጣጫ በቀየረበት አፋር ክልል ደግሞ ዜጎች እንዲፈናቀሉና ንብረታቸው እንዲወንድም ከማድረጉ ባለፈ የደረሱ ምርቶችን ከጥቅም ውጪ አድርጓል።