የሀገር ውስጥ ዜና

ለታላቁ ህዳሴ ግድብ በልደታ ክ/ከተማ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ከ71 ሚሊየን ብር በላይ ተሰበሰበ

By Feven Bishaw

September 15, 2020

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 5 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ከአዲስ አበባ ከተማ ልደታ ክፍለ ከተማ በአንድ ወር ብቻ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ከ71 ሚሊየን ብር በላይ መሰብሰቡ ተገለፀ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ልደታ ክፍለ ከተማ የህዳሴ ግድብ ዋንጫን ለአራዳ ክፍለ ከተማ ያስረከበ ሲሆን÷ በዚህ ወቅት የአዲስ አበባ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት አስተባባሪ አቶ ጃንጥራር አባይን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል፡፡