የሀገር ውስጥ ዜና

ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ለተለያዩ የስራ ኃላፊዎች ሹመት ሰጡ

By Tibebu Kebede

September 15, 2020

አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳድር ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ አዳዲስ ሹመቶች እና የስራ ምደባ ሰጥተዋል።

የተጀመረውን ለውጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል እና በተለያዩ ግዜያት የሚነሱ የህዝብ ቅሬታዎችን ለመመለስ የአመራር ሽግሽግና አዳዲስ የስራ ስምሪት መስጠት አስፈላጊ መሆኑ ለ8 አመራሮች ምደባ መሰጠቱ ተነግሯል።