የሀገር ውስጥ ዜና

በኦሮሚያ ክልል የኮሮና ቫይረስን በመከላከል ትምህርትን ለማስቀጠል እንዲቻል ከ32 ሺህ በላይ ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎች መገንባታቸውን ተገለፀ

By Tibebu Kebede

September 15, 2020

አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኦሮሚያ ክልል የኮሮና ቫይረስን በመከላከል ትምህርትን ለማስቀጠል እንዲቻል 32 ሺህ 108 ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎች መገንባታቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።

የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ቶላ በሪሶ ዛሬ በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፥ በክልሉ ተጨማሪ 30 ሺህ ክፍሎችን ለመገንባት ታቅዶ ከእቅዱ በላይ 32 ሺህ 108 መገንባቱን አስታውቀዋል።