የሀገር ውስጥ ዜና

ጣና ሀይቅ ሞልቶ ባስከተለው ጎርፍ መጥለቅለቅ በምስራቅ ደንቢያ ወረዳ ከ5 ሺህ በላይ ነዋሪዎች ተፈናቀሉ

By Tibebu Kebede

September 15, 2020

አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ጣና ሀይቅ ሞልቶ ባስከተለው የጎርፍ መጥለቅለቅ በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ምስራቅ ደንቢያ ወረዳ ከ5 ሺህ በላይ ነዋሪዎች ከመኖሪያ ቤታቸው ተፈናቅለዋል።

በምስራቅ ደንቢያ ወረዳ አዲስጌ ድጌ፣ አቸራ፣ ሰራባ ፣ ዳብሎና ጣና ወይን ቀበሌዎች 935 አባዎራና እማውራ ጣና በመሙላቱ ተፈናቅለዋል።