የሀገር ውስጥ ዜና

የሰላም ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል በአፋር ክልል በጎርፍ አደጋ ጉዳት የደረሰባቸውን አካባቢዎችን ጎበኙ

By Tibebu Kebede

September 15, 2020

አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል የተመራ ቡድን በአፋር ክልል በጎርፍ አደጋ ጉዳት የደረሰባቸውን አካባቢዎች የዘዋውረው ጎብኝተዋል።

በጉብኝቱም በአፋር ክልል በአዋሽ ወንዝ ከመጠን ባለፈ መጨመር ምክንያት ህይወታቸውና ንብረታቸው ለአደጋ የተጋለጡ ዜጎቻችንን ሁኔታ ተዘዋውረው ተመልክተዋል።