ቢዝነስ

የጥቃቅንና አነስተኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች ምርቶቻቸውን እንዲያሳድጉ የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ

By Meseret Demissu

September 15, 2020

አዲስ አበባ፣ መስከረም 5 ፣2013 ( ኤፍ.ቢ.ሲ) የጥቃቅንና አነስተኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች ምርቶቻቸውን የማሳደግ ዓላማ ያለው የገንዘብ ድጋፍ ስምምነት ተደርጓል።

የገንዘብ ድጋፍ ስምምነቱ የተደረገው በኢትዮጵያ ንግድ እና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት፣ ፕሪሳይስ ኢንተርናሽናል ኮንሰልታንትና የፈጠራ ድርጅት እንዲሁም የግሪን ኢትዮጵያ ማኑፋክቸሪንግ ፕሮጀክት ተጠቃሚ ኢንተርፕራይዞች መካከል መሆኑ ተገልጿል።