የሀገር ውስጥ ዜና

የቱሪስት መዳረሻዎችን የማልማት ስራዎች ቱሪዝምን በማነቃቃት ሀገራዊ ምጣኔ ሀብት ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተገለፀ

By Feven Bishaw

September 15, 2020

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 5 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) አሁን ላይ የተጀመሩ የቱሪስት መዳረሻዎችን የማልማት ስራዎች ቱሪዝሙን በማነቃቃት ሀገራዊ ምጣኔ ሀብት ለማሳደግ የሚጫወቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ።

ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉት የምጣኔ ሃብት ጉዳዮች መምህርና ተመራማሪ ዶክተር ንጉሴ ስሜ፥ አሁን ላይ የተጀመሩ የቱሪስት መዳረሻዎችን የማልማት እና የማሳደግ ስራዎች ኢንቨስትመንትን እንደሚያነቃቃ ገልጸዋል።