የሀገር ውስጥ ዜና

በ24 ሰዓታት 700 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው፤ የ13 ሰዎች ሕይወት አልፏል

By Tibebu Kebede

September 15, 2020

አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 10 ሺህ 24 የላብራቶሪ ምርመራ 700 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።

በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 65 ሺህ 486 መድረሱንም ሚኒስቴሩ ያወጣው እለታዊ መረጃ ያመለክታል።