የሀገር ውስጥ ዜና

ሠሞኑን በመተከል ዞን አንዳንድ አካባቢዎች የተፈጠረውን የጸጥታ ችግር የማረጋጋትና የሕግ የበላይነት የማስከበር ሥራ በትኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ

By Meseret Demissu

September 16, 2020

አዲስ አበባ ፣መስከረም 6 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ከሠሞኑ በመተከል ዞን አንዳንድ አካባቢዎች የተፈጠረውን የጸጥታ ችግር የማረጋጋትና የሕግ የበላይነት የማስከበር ሥራ የክልሉ ሠላም ግንባታ እና ጸጥታ ቢሮ ከመከላከያ ሠራዊት እና ከፌዴራል ፖሊስ ጋር በመቀናጀት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጿል።

በዚህም ተፈጥሮ የነበረው የጸጥታ ችግር ወደ አንጻራዊ ሠላም በመመለስ ላይ መሆኑንም ቢሮው አስታውቋል፡፡