አዲስ አበባ፡ መስከረም 6 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መሥተዳድር ዶክተር ፋንታ ማንደፍሮ በጣና ሐይቅ ሞልቶ መፍሰስ ምክንያት በውኃ የተከበቡና የተጥለቀለቁ የፎገራ ወረዳ አካባቢዎችን ሁኔታ በአካል ተገኝተው ተመልክተዋል።
በደቡብ ጎንደር ዞን ፎገራ ወረዳ ዋገጠራ፣ ስንደዬ፣ አባጋሹ፣ ባርጌና ሴላድባ፣ ማርያም ምድር እና አጎራባች አካባቢዎች ያሉ ነዋሪዎች የመኖሪያ ቀያቸውና የእርሻ ማሳቸው በውኃ ተከቧል ።