ዓለምአቀፋዊ ዜና

በኢትዮጵያና በኢንዶኔዥያ የቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላኖች አደጋ ኩባንያውና ተቆጣጣሪው ባለስልጣን ተጠያቂ ተደረጉ

By Abrham Fekede

September 16, 2020

አዲስ አበባ፣ መስከረም 6፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያና በኢንዶኔዥያ በተከሰከሱት ሁለት ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላኖች አደጋ የአውሮፕላን አምራቹ ቦይንግና የፌደራል አቪዬሽን ባለስልጣን አካላት ተጠያቂ ተደረጉ፡፡

ምርመራውን ለ18 ወራት ሲያካሂድ የቆየው የአሜሪካ ምክርቤት ቦይንግ ቴክኒካል የሆኑ ጉዳዮችን ለማጋራት ዳተኛ ነበር ብሏል፡፡