የሀገር ውስጥ ዜና

በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓታት 738 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው 10 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል

By Tibebu Kebede

September 16, 2020

አዲስ አበባ፣ መስከረም 6፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገ 8 ሺህ 355 የላቦራቶሪ ናሙና ምርመራ 738 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል።

በአጠቃላይ እስካሁን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 66 ሺህ 224 ደርሷል።