አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 11፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይ.ኤም.ኤፍ) ለኢትዮጵያ ያፀደቀው የገንዘብ ድጋፍ የማክሮ ኢኮኖሚ ሚዛኑን ለማስተካከል እንደሚረዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ገለፁ።
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይ.ኤም.ኤፍ) ሥራ አስፈፃሚ ቦርድ ለኢትዮጵያ የ2 ነጥብ 9 ቢሊየን ዶላር ድጋፍ ማጽደቁን ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በፌስቡክ ገጻቸው ባስተላለፉት መልእክት ይህንን ያሉት።