የሀገር ውስጥ ዜና

የብር ኖት ላይ ለውጥ መደረጉ ኮንትሮባንድን ለመቀነስ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ተገለፀ

By Feven Bishaw

September 17, 2020

አዲስ አበባ፣ መስከረም 7፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የብር ኖት ላይ ለውጥ መደረጉ በብርም ሆነ በውጭ ሀገር ገንዘብ የሚደረገውን ኮንትሮባንድ ለመቀነስ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረው የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ።

የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ ከፋና ብሮድካስቲን ኮርፖሬት ጋር ባደረጉት ቆይታ እንዳሉት፥ የብር ኖቱ ለውጥ በኮንትሮባንድ ይገቡ የነበሩ እና ህብረተሰቡን ለተለያዩ የጤና እና የደህንነት ችግር የሚየጋልጡ ህገውጥ ተግበራትን ይቀንሳል።