የሀገር ውስጥ ዜና

የመስቀል በዓልን ምክንያት ያደረገ ጉዞ ማድረግ አይገባም – አቶ ርስቱ ይርዳው

By Feven Bishaw

September 18, 2020

አዲስ አበባ፣ መስከረም 8፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ)የመስቀል በአልን ምክንያት ያደረገ ጉዞ ማድረግ እንደማይገባ የደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ርስቱ ይርዳው ተናገሩ፡፡

ምክትል ርእስ መስተዳደሩ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር በነበራቸው ቆይታ፥ በክልሉ በደማቁ የሚከበረውን የመስቀል በአልን ተከትሎ መሰባሰቦች ለኮሮና ቫይረስ ስርጭት ምክንያት እንዳይሆን በዓመት አንድ ጊዜ ወደ ቤተሰብ የሚሰባሰበው በርካታ ህዝብ ዘንድሮ ባለበት እንዲያከብር አሳስበዋል ።