የሀገር ውስጥ ዜና

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲና ብሄራዊ የመረጃ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በጋር ለመስራት የስምምነት ሰነድ ፈረሙ

By Feven Bishaw

September 18, 2020

አዲስ አበባ፣ መስከረም 8፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ)አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲና ብሔራዊ የመረጃ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በትምህርት፣ በሥልጠናና በአቅም ግንባታ ዘርፍ ተባብረው ለመሥራት የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ መፈራረማቸው ተገለፀ።

በብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ሥር የሚገኘው ብሔራዊ የመረጃ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በመረጃና ደህንነት ዘርፍ ብቁ የሰው ሃይል ለማፍራት ፣ ከአገርና ከህዝብ የተሰጠውን ተልዕኮ በብቃት ለመወጣት እና የተጀመረውን ጥረት ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በትምህርት ፣ በጥናትና ምርምር እንዲሁም ሙያዊ ክህሎትን ለማሳደግ በሚያስችሉ ዘርፎች ላይ በትብብር ለመሥራት ከስምምነት ላይ ደርሷል።