የሀገር ውስጥ ዜና

አለም አቀፉን የፅዳት ቀን በንቅናቄ ለማሳለፍ ዝግጅት ተደርጓል- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር

By Feven Bishaw

September 18, 2020

አዲስ አበባ፣ መስከረም 8፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ)አለም አቀፉን የፅዳት ቀን በንቅናቄ ለማሳለፍ ዝግጅት መደረጉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ።

የአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር አወቀ ሀይለማርያም እና የደረቅ ቆሻሻ አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ስራ አስኪያጅ ዶክተር እሸቱ ለማ በጋራ በሰጡት መግለጫ፣ በነገው እለት የሚከበረውን የአለም አቀፍ የፅዳት ቀን በፅዳት ንቅናቄ ለማሳለፍ ዝግጅት መደረጉን ገልፀዋል።