የሀገር ውስጥ ዜና

የሀዲያ ዘመን መለወጫ በዓል “ያሆዴ” እየተከበረ ነው

By Meseret Demissu

September 20, 2020

አዲስ አበባ፣ መስከረም 10 ፣ 2013(ኤፍ.ቢ.ሲ)የሀዲያ ዘመን መለወጫ “ያሆዴ” ክብረ በዓል በሀዲያ ዞን እየተከበረ መሆኑን የዞኑ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ አስታውቋል።

የዘመን መለወጫ በዓሉ የሀይማኖት አባቶች፣የሀገር ሽማግሌዎች እና የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በተለያዩ ክንዋኔዎች በመከበር ላይ መሆኑን ከዞኑ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።