የሀገር ውስጥ ዜና

የግብርና ሚኒስትር አቶ ዑመር ሁሴንን ጨምሮ የፋኦ የኢትዮጵያ ተወካይ በአፋር ክልል የበረሃ አንበጣ ያለበትን ሁኔታ ተመለከቱ

By Tibebu Kebede

September 21, 2020

አዲስ አበባ፣ መስከረም 11፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የግብርና ሚኒስትር አቶ ዑመር ሁሴን ፣ ሚኒስትር ዴኤታ ማንደፍሮ ንጉሴን እና የዓለም የምግብ እና እርሻ ድርጅት (ፋኦ) የኢትዮጵያ ተወካዮች በአፋር ክልል የበረሃ አንበጣ ያለበትን ሁኔታ እና እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎችን ተመልክተዋል።

በጉብኝቱ የተሳተፉ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች እና የዓለም የምግብ እና እርሻ ድርጅት (ፋኦ) ተወካዮች የበረሃ አንበጣን ለመቆጣጠር እየተከናወነ የሚገኘው ስራ መጠናከር እንዳለበት ገልፀዋል።