የሀገር ውስጥ ዜና

በመሬት መንሸራተት ተዘግቶ የነበረው የአዋሽ ድሬዳዋ መንገድ ዳግም ለተሽከርካሪ ክፍት መሆኑ ተገለፀ

By Meseret Demissu

September 21, 2020

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 11 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በመሬት መንሸራተት ምክንያት ተዘግቶ የነበረውከአዋሽ ወደ ድሬዳዋ የሚዘልቀው መንገድ ዳግም ለተሽከርካሪ ክፍት መሆኑ ተገልጿል።

በኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የድሬዳዋ ድስትሪክት ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር አንድነት ሰይፉ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮረፖሬት እንደገለፁ፥ ከድሬዳዋ 117 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በቦርዳ እና ካራ ሚሊ መካከል በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት መሬት ተንሸራቶ ከቅዳሜ ምሽት ጀምሮ ዋናው መንገድ ተዘግቶ መቆየቱን አስታውሰዋል።