የሀገር ውስጥ ዜና

በጋምቤላ ክልል በዓመት እስከ 17 ሺህ ቶን የአሳ ምርት ለማምረት የሚያስችል ስምምነት ተደረገ

By Meseret Demissu

September 22, 2020

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 12 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በጋምቤላ ክልል እስከ 17 ሺህ ቶን የአሳ ምርት ለማምረት የሚያስችል ስምምነት ተፈርሟል ።

በክልሉ የሚገኘውን እምቅ የአሳ ሀብት ልማት ለማሳደግ የሚያስችል ፕሮጀክት ስምምነት በጋምቤላ ክልል፣ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና በጋምቤላ ዩኒቨርስቲ መካከል ተደርጓል።