አዲስ አበባ ፣ መስከረም 12 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በመተከል ዞን የሚስተዋሉ የጸጥታ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ከነገ ጀምሮ በሁሉም ወረዳዎች የአመራር ግምገማ እንደሚካሄድ ተገልጿል።
በቅርቡ የጸጥታ ችግር የተፈጠረባቸውን ወምበራና ቡለን ወረዳዎች ጨምሮ በመተከል ዞን ሁሉም ወረዳዎች ዘላቂ ሠላምን ለመገንባትና የልማት ሥራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል ያለመ የአመራር ግምገማ እንደሚካሄድ ነው የክልሉ መንግስት ያስታወቀው።