የሀገር ውስጥ ዜና

26 ባለሃብቶችን የያዘ የሱዳን የልዑካን ቡድን በኢትዮጵያ ጉብኝት እያደረገ ነው

By Meseret Demissu

September 22, 2020

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 12 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በሱዳን የሚገኙና በቱሪዝም ዘርፉ የተሰማሩ 26 ባለሃብቶችን የያዘየልዑካን ቡድን በኢትዮጵያ ጉብኝት እያደረገ ነው።

ሱዳንና ኢትዮጵያን በኢንቨስትመንት ተግባራት በማስተሳሰር የህዝቦችን የጋራ ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን በሱዳን የኢትዮጵያ አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ ተናግረዋል።