የሀገር ውስጥ ዜና

ዓለም አቀፍ የቱሪዝም ቀን በዓልን ለማክበር የክልል ርዕሳነመስተዳድራን ጅግጅጋ ገብተዋል

By Meseret Awoke

September 27, 2020

አዲስ አበባ፣ መስከረም 17፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ)ዓለም አቀፍ የቱሪዝም ቀን በዓልን ለማክበር የክልል ርዕሳነመስተዳድራን ጅግጅጋ ከተማ ገብተዋል፡፡

የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳው፣ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሒሩት ካሳሁን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ናቸው ወደ ጅግጅጋ ያመሩት፡፡