ኮሮናቫይረስ

በቅርቡ ይፋ በሚደረገው የመመርመሪያ መሳሪያ የኮሮና ቫይረስ ውጤትን በደቂቃዎች ውስጥ ማወቅ ይቻላል – የዓለም ጤና ድርጅት

By Abrham Fekede

September 29, 2020

አዲስ አበባ፣ መስከረም 19፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የዓለም ጤና ድርጅት በቅርቡ ይፋ የሚያደርገው የኮሮና ቫይረስ የመመርመሪያ መሳሪያ በደቂቃዎች ውስጥ ውጤትን ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡

የድርጅቱ ዳይሬክተር ጄነራል ቴድሮስ አድሓኖም÷ ቫይረሱን ለመዋጋት በሚደረገው ጥረት አዲሱ መመርመሪያ መልካም ዜና ይዞ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡