የሀገር ውስጥ ዜና

የፌዴራል መንግስቱ ህጋዊነት ከከሰረው ቡድን ቅዥት ሳይሆን ከህገ መንግስቱ እና ከኢትዮጵያ ህዝቦች የመነጨ ነው – ዶክተር ዓለሙ ስሜ

By Abrham Fekede

September 29, 2020

አዲስ አበባ፣ መስከረም 19፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና ሲቪክ ማህበራት ዘርፍ ኃላፊ ዶክተር አለሙ ስሜ የፌዴራል መንግስቱ ህጋዊነት ከከሰረው ቡድን ቅዥት ሳይሆን ከህገ መንግስቱ እና ከኢትዮጵያ ህዝቦች የመነጨ መሆኑን ገለጹ፡፡

ዶክተር አለሙ ስሜ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ባደረጉት ቆይታ÷ በኢትዮጵያ መስከረም 25ም ሆነ ከዚያ በኋላ ጠንካራ እና ህጋዊ መንግስት አለ ይኖራልም ብለዋል።