አዲስ አበባ ፣ መስከረም 21 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአፋር እና ሶማሌ ክልሎች የተከሰተውን የበረሃ አንበጣ ባለበት ለመቆጣጠርና ወደ አማራ፣ ኦሮሚያ እና ትግራይ ክልሎች በመዛመት ሰብል ላይ ጉዳት እንዳያደርስ እየተሰራ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
በአሁኑ ወቅት የበረሃ አንበጣው በአፋር ክልል በ26 ወረዳዎችና በምስራቅ አማራ አጎራባች ወረዳዎች እና በሶማሌ ክልል በሲቲ ዞን በሚገኙ በአይሻ፣ አወበሬ እና ሽንሌ ወረዳዎች ዳግም ተከስቷል ነው ያለው ሚኒስቴሩ፡፡