የሀገር ውስጥ ዜና

ትምህርት ሚኒስቴር በሀገር አቀፍ ደረጃ የመምህራንን ቀን ለማክበር መዘጋጀቱን አስታወቀ

By Feven Bishaw

October 01, 2020

አዲስ አበባ ፣መስከረም 21 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ከዘንድሮ ጀምሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ የመምህራን ቀን እንዲከበር መወሰኑን የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

የትምህርት ሚኒስትር ዲኤታ ዶክተር ገረመው ሁሉቃ መምህራን ትውልድን በመቅረፅ ውስጥ ትልቅ ሚና ስላላቸው ለመምህራን አስፈላጊውን እውቅና እና ክብር መስጠት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡