ስፓርት

አትሌት ለተሰንበት ግደይ አቀባበል ተደረገላት

By Abrham Fekede

October 09, 2020

አዲስ አበባ፣ መስከረም 29፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በስፔን ቫሌንሺያ የሴቶችን የ5 ሺህ ሜትር ክብረወሰን የሰበረችው አትሌት ለተሰንበት ግደይ አቀባበል ተደረገላት፡፡

ለተሰንበት ከዋና አሰልጣኟ ኃይሌ እያሱ ጋር ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ስትደርስ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት ደራርቱ ቱሉ፣ አትሌት ማርቆስ ገነቴ የኢትዮጵያ አትሌቶች ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ ቢልልኝ መቆያ የፌዴሬሽኑ ፅህፈት ቤት ኃላፊ በስፍራው ተገኝተው አቀባባል አድርገውላታል፡፡