ዓለምአቀፋዊ ዜና

የዓለም ባንክ ለታዳጊ ሃገራት ለኮቪድ19 ክትባት የሚውል 12 ቢሊየን ዶላር አጸደቀ

By Abrham Fekede

October 14, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 4፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የዓለም ባንክ ለታዳጊ ሃገራት የኮሮና ቫይረስ ክትባት የሚውል 12 ቢሊየን ዶላር አጸደቀ፡፡

ባንኩ ሃገራቱን በፋይናንስ የደገፈው ክትባቱ ዝግጁ በሚሆንበት ወቅት እንዲገዙበት እና እንዲያሰራጩበት እንዲሁም ለዜጎቻቸው ለኮሮና ቫይረስ ምርመራ እና ክትትል እንዲያውሉት ነው ተብሏል፡፡