የሀገር ውስጥ ዜና

ሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ከጥቅምት 23 እስከ 30 የመጀመሪያ ዙር የተማሪዎች ቅበላ እንደሚያደርጉ ተገለጸ

By Abrham Fekede

October 17, 2020

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 7፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዶክተር ሳሙኤል ኡርቃቶ ሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ከጥቅምት 23 እስከ 30 አስፈላጊውን ዝግጅት በማጠናቀቅ የመጀመሪያ ዙር የተማሪዎች ቅበላ እንዲያደርጉ አሳሰቡ፡፡

ሚኒስትሩ በቅርቡ በኮቪድ-19 ፕሮቶኮል መሠረት በተካሔደው የተቋማት ድጋፍና ምልከታ ውጤት በአንዳንድ ተቋማት የታዩ ክፍተቶች በፍጥነት ተሟልተው በግልጽ መርሃ-ግብር ለተማሪዎች ቅበላ እንዲያደርጉ አሳስበዋል፡፡