አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 10፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት በምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ አቅራቢነት ልዩ ልዩ ሹመቶችን አጸደቀ።
በዚህ መሠረት፦
1ኛ. አቶ ጥራቱ በየነ – በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማ ስራ አስኪያጅ ቢሮ ኃላፊ
2ኛ. ዶክተር መስከረም ፈለቀ – ቤቶች ልማት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ
3ኛ . ኢንጂነር አያልነሽ ሀ/ማርያም – ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ
4ኛ. ዶክተር መስከረም ምትኩ – የፕላን ኮሚሽን ኮሚሽነር
5ኛ. ዶክተር ሚልኬሳ ጃጋማ – መሬት ልማት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ
6ኛ. ዶክተር ሙሉቀን ሀብቱ – ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ
7ኛ. አቶ ተፈራ ሞላ – ሰራተኛና ማህበራዊ ቢሮ ኃላፊ
8ኛ. አቶ ሙሉጌታ ተፈራ – ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል።