Fana: At a Speed of Life!

የማክሮ ኢኮኖሚ ኮሚቴ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በተገኙበት ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 11፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የማክሮ ኢኮኖሚ ኮሚቴ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት ተካሄደ።
በስብሰባው በመጀመሪያው ሩብ ዓመት ከውጪ ንግድ የተገኘውን ገቢ፣ የዋጋ ግሽበት እና ተያያዥ እርምጃዎች፣ የመንግሥት ገቢ እና የሥራ ክንውን ሁኔታ መገምገሙን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፌስቡክ ገፃቸው ላይ አስፍረዋል።
እንዲሁም ለተያዘው ዓመት በተለዩ ዐበይት ቀዳሚ ጉዳዮች መሠረት፤ ኮሚቴው ለቀጣይ ሩብ ዓመት የሚሆኑ ግቦችን ለይቶ ቀጣይ አቅጣጫ አስቀምጧል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.