የሀገር ውስጥ ዜና

በከተሞች የሚስተዋለውን ሰፊ የስራ እድል ክፍተት ለመፍታት የሚያግዝ ስትሬቴጅያዊ እቅድ ተዘጋጀ

By Tibebu Kebede

December 25, 2019

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 15፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በከተሞች የሚስተዋለውን ሰፊ የስራ እድል ክፍተት ለመፍታት የሚያግዝ ስትሬቴጅያዊ እቅድ መዘጋጀቱን የከተማ ልማትና ኮንስትራክሸን ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

በቀጣዮቹ አስርት አመታት ይተገበራል ተብሎ የሚጠበቀው የከተማ ልማት መሪ እቅድ አካል የሆነው ይህ ስትራቴጅ በከተሞች ያለውን የስራ አቅም በጥናት ለይቷል፡፡