የሀገር ውስጥ ዜና

የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን በሶስት ዓመት ለማጠናቀቅ ጥረት እየተደረገ ነው

By Meseret Demissu

October 22, 2020

አዲስ አበባ ፣ጥቅምት 12 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን በሶስት ዓመት ለማጠናቀቅ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የውሃ፣ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ገለፁ።

2 ሺህ 160 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም ያለው የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ግድብ በኢትዮጵያ ከሕዳሴ ግድብ ቀጥሎ ሁለተኛው ግዙፍ ፕሮጀክት ነው።